የእንጅባራ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ ፕሮግራም አደገ።

አሁን ላይ መንግስት በዘረጋው የመምህራን ትምህርት ኮሌጆች የደረጃ ሽግግር እንጅባራ መምህራን ትምህርት ኮሌጅ ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ መርሃ ግብር ማደግ ችሏል።
ህዳር 11/2015(አዊ ኮሙኑኬሽን) ዛሬ የኮሌጁ ይፋዊ የዲግሪ ፕሮግራም ማስጀመሪያ መርሃ ግብርና የሴት ተማሪዎች ዶርሚታሪ ማስመረቅ ፕሮግራም ተከናውኗል።
በፕሮግራሙ የአብክመ ትምህርት ቢሮ ም/ሀላፊ አቶ መኳንንት አደመ፣የአዊ ብሄ/አስ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንግዳ ዳኛው ፣የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ጋርዳቸው ወርቁ ፣ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና የሀገር ሽማግሌዎችን ጨምሮ ኮሌጁ ያለበትን ደረጃ ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
በበላይነሽ አበበ